ስለ ድረ ገጹ
እንኳን ወደ ነገደ ጎበዜ ቤተ መዝገብ በደህና መጡ
- በዚህ ድረ ገጽ ውስጥ ተሰባስበው የቀረቡት ጽሁፎች፣ በአብዝኛው ከነገደ የግል ማህደር የተገኙ ናቸው። ጽሁፎቹም አንዳንዶቹ በስሙ የተፈረሙ፣ አንዳንዶቹ በብእር ስም የወጡ ሌሎቹ ደግሞ ያልተፈረሙባቸው ይገኙበታል።
- የጽሁፎቹ አርእስትና ቀን ፣እንዲሁም ጽሁፉ የወጣበትን መጽሄት፣ ጋዜጣ፣ ድርጅት፣ ማህበር ወዘተርፈ፣ ዝርዝሩን መዝግቦ ስላስቀመጠው ፣ ጽሁፎቹን ማሰባሰብና ማቀናጀት ቀላል ነበር ማለት ይቻላል።
- ድረገጹ የተዘጋጀው በቤተሰቡ ሲሆን የቀረበውም እንደ ግል ቤተ መዝገብ/ቤተ መጽሃፍት በዋናነት ለልጆቹና ለልጅ ልጆቹ፣ የአባታቸውን፣ የአያታቸውን ታሪክ እንዲያውቁት ለማስተላለፍ የታቀደ ነው።
- በተጨማሪ፣ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪዎች፣ የታሪክ ተመራማሪዎች ለሚያደርጉት ጥናት፣ምርምርም ሆነ ትንተና እንደ መረጃ/ ማገናዘቢያ (reference) በተወሰነ ደርጃ አስተዋጽኦ ያደርጋል በለን ተስፋ እናደርጋለን።
- መረጃ ማሰባሰብና ተደራሽ ማድረግ፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ እውቀትን ለማዳበር የረዳል የሚል ጽኑ እምነት አለን።
- በዚህ ድረ ገጽ ላይ የተሰበሰበውን ሰነድ ምንጩ እስከተጠቀሰ ድረስ ለትርፍ ላልሆነ ዓላማ መጠቀም ይቻላል። ይህንን በሚያደርጉበት ጊዜ “ከነገደ ጎበዜ የግል መዘገብ የተገኘ - www.negedegobezie-archives.com» የሚለውን ሃረግ እንዲጨምሩ በትህትና እንጠይቃለን።
- ይህንን ድረ ገጽ ለማዘጋጀት፣ ሰነዶችን በማፈላለግ ለረዱን በዋሽንግተን ዲሲ፣ በስዊድን፣ በጀርመን፣ በቤልጅየም፣በኢትዮጵያ ለሚገኙት ወዳጆቻችንን የልብ ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን።
ስለ
እንኳን ወደ ነገደ ጎቤዚ ማህደር ቦታ በደህና መጡ።
